ታክስ መክፈል ካለበት የህብረተሰብ ከፍል ውስጥ 60 በመቶው ብቻ እየከፈለ ይገኛል – የገቢዎች ሚኒስቴር

በኢትዮጵያ ታክስ መክፈል ካለበት የህብረተሰብ ክፍል ውስጥ 60 በመቶው ብቻ ታክስ እየከፈለ እንዳለ የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ።

ይህ የተገለጸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለሰራተኞቹ የአቅም ግንባታ ስልጠና መድረክ ባዘጋጀበት ወቅት የገቢዎች ሚኒስትሯ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ከጋዜጠኖች ጋር ባደረጉት ቆይታ ነው፡፡

የታክስ አሰባሰብ ሂደቱ ላይ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመፍታት የገቢ አሰባሰብን ለማዘመን ታህሳስ 12 2011 ዓ.ም የተከፈተውን ሀገራዊ የታክስ አሰባሰብ ንቅናቄ ስኬታማ እንደሆነ ሚኒስትሯ ገልጸዋል፡፡