በዶሃ የተሳተፈው የአትሌቲክስ ቡድን አዲስ አበባ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት

ለ17ኛ ጊዜ በኳታር ዶሃ በተካሄደው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የተሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን አዲስ አበባ ገብቷል፡፡

ዛሬ ከማለዳው 1፡30 ላይ አዲስ አበባ ቦሌ ኤርፖርት ሲደርስ የኢ.ፌ.ድ.ሪ. ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚነኒስትር ዶ/ር ሂሩት ካሳው፣ የኢ.ፌ.ድ.ሪ. ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚነኒስትር ዴኤታ አቶ ሀብታሙ ሲሳይ፣ የኢ.ፌ.ድ.ሪ. ስፖርት ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር አቶ ጌታቸው ባልቻ፣ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክሰ ፌዴሬሽን ም/ፕሬዝዳንት አትሌት ገ/እግዚአብሄር ገ/ማርያም እንዲሁም የአትሌቲክስ የሙያ ማህበራትና ክለብ አመራሮችን ጨምሮ የስፖርት ቤተሰቡ በተገኘበት ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል፡፡

ቡድኑ በቆይታው ሁለት ወርቅ ፣ አምስት ብር እና 1 ነሃስ በድምሩ 8 ሜዳሊያዎችን በማግኘት ከዓለም 5ኛ ከአፍሪ 2ኛ በመሆን ውድድሩን ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡