ጥር 27/2014 (ዋልታ) የሶማሊያ ፕሬዝዳንት መሀመድ አብዱላሂ ፋርማጆ በ35ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ለመሳተፍ ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል።
ፕሬዝዳንቱ በቦሌ ዓለም ዐቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የግብርና ሚኒስትሩ ኡመር ሁሴን አቀባበል አድርገውላቸዋል።
በተጨማሪም የመከላከያ ማርች ቡድን፣ ከየክልሉ የመጡ የባህል ቡድን አባላት እንዲሁም ሰርከስ አቅራቢ ወጣቶች በአቀባበል ስነሥርዓት ላይ የተለያዩ ጥዑመ ዜማ በማሰማት መቀበላቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
35ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ “የአፍሪካ አኅጉርን የሥርዓተ ምግብ አቅም መገንባት፤ የሰው ሃብት ልማት፣ የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ልማትን ያፋጥናል” በሚል መሪ ሃሳብ ቅዳሜና እሁድ ይካሄዳል።
ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://www.facebook.com/waltainfo
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!