ሰኔ 2/2014 (ዋልታ) ለትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን አዲስ የሥራ አመራር የቦርድ አባላት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተሹመዋል።
ባለስልጣኑ ሰኔ 1 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጸሕፈት ቤት በተላከ ደብዳቤ አዲስ የሥራ አመራር የቦርድ አባላት እንደተመደበለት አስታውቋል።
በዚህም ፡-
? የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል – ሰብሳቢ
? የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) – አባል
? የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) – አባል
? የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋዬ ዳባ – አባል
? የኢንፎርሜሽ መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ሹመቴ ግዛው (ዶ/ር) – አባል
? የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳህረላ አብዱላሂ – አባል
? የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተዶክተር አንዱዓለም አድማሴ አባልና ጸሀፊ ሆነው ተሸመዋል፡፡