ኢትዮጵያና የዓለም ባንክ የ600 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ

ሰኔ 17/2014 (ዋልታ) ኢትዮጵያ እና የዓለም ባንክ የ600 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ።

ከ600 ሚሊየን ዶላር ውስጥም 200 ሚሊየን ዶላሩ በድጋፍ መልክ የተገኘ ነው ተብሏል፡፡

400 ሚሊየን ዶላሩ በብድር መልክ የተገኘ መሆኑን ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

ገንዘቡ በሀገሪቱ የምግብ ሥርዓትን ለማሻሻል እንደሚውል ተጠቁሟል፡፡