ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ 2 ሺህ ከሚበልጡ የደኢህዴን ከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያዩ

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደኢህዴን/ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አድርገዋል።

በትናንትናው እለት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት በተካሄደው የውይይት መድረክ ላይም 2 ሺህ 400 የደኢህዴን ከፍተኛ አመራሮች መካፈላቸው ተገልጿል።

በውይይት መድረኩ ላይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ሥልጠና እና ገለፃ ማድረጋቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

በተጨማሪም በመቻቻል፣ በመከባበር እና በሌሎች የኢትዮጵያ እሴቶች ዙሪያም ለመድረኩ ተሳታፊዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል።(ኤፍቢሲ)