እንጂነር ስመኘው በቀለ እራሳቸውን ማጥፋታቸውን ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ

  የታላቁ  ህዳሴ  ግድብ  ዋና  ሥራ አስኪያጅ  እንጂነር  ስመኘው  በቀለ እራሳቸውን   ማጥፋታቸውን  ፖሊስ  ባደረገው  ምርመራ  ማረጋገጡን  አስታወቀ  ።

የፌደራል  ፖሊስ   ከአዲስ  አበባ  ፖሊስ  ጋር በመተባበር   በዛሬው  ዕለት   ይፋ ባደረገው  መግለጫው  እንደገለጸው   በሐምሌ 19 ፣ 2010 ዓም  ጥዋት  2:30 ሰዓት ላይ  ከዚህ  ዓለም በሞት  የተለዩት  እንጂነር ስመኘው  በቀለ    በራሳቸው  ሽጉጥ  እራሳቸውን  ማጥፋታቸውን የፎረንሲክ  ምርመራ ውጤቱ እንደሚያሳይ ተገልጿል ።

እንጂነሩ  የተኮሱት  ጥይት  በግራ ጆሯቸው  ገብቶ  በቀኝ  ጆሮ  አካባቢ የወጣ መሆኑን የገለጸው ፖሊስ  አደጋው  ኢንጂነሩ  ከሞቱ በኋላ  በመኪናቸው  ውስጥ  ሁለት ፖስታዎች መገኘታቸው  ተመልክቷል ።

የፌደራል  ፖሊስ ኮሚሽነር ዘይኑ ጀማል በመግለጫው ወቅት እንደተናገሩት  እንጂነር ስመኘው  ከመሞታቸው  አንድ ቀን ቀደም ብለው ትልቅ ልጃቸው   ማጥናት እንዳለበትና መረጃ  መገኘቱን  ገልጸዋል ።

በተጨማሪም  ስመኘው  ጠዋት ላይ ቢሮ መገኘታቸውና ለሁለት ሹፎሮቻቸውና ለጸሓፊያቸው ስልክ ጭምር   በመደወል  በፖስታ  የታሸገ ማስታወሻ እንዲሰጥላቸው   ማድረጋቸውን ያነሱት ኮሚሽነሩ  ኢንጂነሩ  በምን  ምክንያት እንደሞቱ በትክክል የሚያስቀምጡ  አለመሆናቸው ግን አያይዘው ገልጸዋል ።  

እንጂነሩ  በምን  ምክንያት  ሞቱ  የሚለውን  ለወደፊቱ  ይበልጥ  በዝርዝር  ምርመራ  የሚደረግበት  መሆኑ   የጠቆሙት ኮሚሽነሩ   የግድቡ  ግንባታ  በተፈለገው  ደረጃ አለመድረስና እስካሁን  የወጣው  ወጪ ከፍተኛ መሆን  እራሳቸውን ለማጥፋት ምክንያት  እንደሆነ በጥርጣሬ  አስቀምጠዋል ።