ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከቡራዩ ከተማና አካባቢው ተፈናቅለው በመድሃኒዓለም ትምህርት ቤት ተጠልለው የሚገኙ ዜጎች ጎብኝተዋል ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ባደረጉት ወቅት ተፈናቃዮቹ ስላጋጠማቸው አደጋና ስለተፈጸመው ሁኔታ ለጠቅላይ ሚንስትሩ አስረድተዋል ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድም ተፈናቃዮቹን ባጋጠማቸው ሁኔታና በደረሰባቸው አደጋ እጅግ ማዘናቸውን በጉብኝታቸው ወቅት ገልፀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩም በዚህ ድርጊት ፈፃሚዎች ተጠያቂ እንዲሆኑና ድርጊቱን እንዳይደገም መንግስት ጠንካራ እርምጃ እንደሚወስድ ተናግረዋል ።
ከቡራዩ የተፈናቀሉ ዜጎችም ወደ ቀያቸው በፍጥነት እንዲመለሱና እንዲቋቋሙ መንግሥት የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግም ቃል ገብተዋል።