ኦህዴድ ስያሜውን ወደ ኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ቀየረ

የኦሮሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ) ስያሜውን ወደ ኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ መቀየሩን አስታወቀ ።

ድርጅቱ በዛሬው ዕለት እያካሄደ ባለው 9ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ  ቀደም ሲል  ሲጠቀምበት  የነበረውን  ስያሜ  ለውጥ በተመለከተ  ውይይት  በማድረግ  ነው  ውሳኔ ያስተላለፈው ።

ድርጅቱ በተያያዘ ቋሚ ኮሚቴው በፖለቲካ፣ ማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚ አጀንዳዎች  ትኩረት አድርጎ ውይይት አድርጓል ።

በዛሬው  ዕለት  በተነሱት የትምህርት ፣ የጤና ተደራሽነትና አገልግሎት  አሠጣጥ  አፈጻጸም ላይ  የተለያዩ ሓሳቦች  ከተሳታፊዎች ተነስተዋል ።

በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ዓመታት የጤና ተደራሽነት ላይ ጠንካራ የሆነ አፈጻጸም  ታይቷል ተብሏል ።

ሆኖም  በባለሙያና በመድሓኒት አቅርቦት ረገድ ሰፊ ክፍተት ታይቷል ያሉት ተሳታፊዎች የቴክኖሎጂ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ተሠጥቶ ሲሰራ ቆይቷል  ብለዋል  ።

የድንበር ወሰንን  የተፈጠሩ ችግሮችን በተመለከተ  በተሳታፊዎች ጥያቄዎች  የተነሱ ሲሆን  የኦህዴድ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ለማ ከሶማሌ ጋር የተከሰተው የወሰን ችግር  የኮንትሮባንዲስቶች  ሴራ መሆኑን  አስረድተዋል ።

ከሶማሌ  ክልል  ጋር  ያለውን ግንኙነት  ይበልጥ  የተሻለ ለማድረግ  አቅጣጫ  ተቀምጦ እየተሠራ እንደሚገኝ  ገልጸዋል  ።

ኦህዴድ የኦሮሞ ህዝብ የማንነት ጥያቄን  ለመመለስም ታሪክ  የማይረሳው  መልካም  ሥራ  መሥራቱንና  ለወደፊቱን  የህዝቡን  ጥያቄዎች በአጭርና በረጅም ጊዜ  ለመፍታትም ድርጅቱን ጥረት  እንደሚያደርግ ተገልጿል ።

ኦህዴድ  ለወጠፊቱን   በለውጥ  ፈላጊ  አመራሩ ጋር  በመሆን  በድርጅቱም ሆነ በአገሪቱ የተሻለ  ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም  ፖለቲካዊ ለውጦች እንዲመዘገቡ በርትቶ እንደሚሠራ   በውይይቱ ተገልጿል ።

በኦሮሚያ ክልል የኦዲት  አፈጻጸሙም  ምን እንደሚመስል  የቁጥጥር ሥራው ምን ያህል ውጤታማ እንደሆነም  በጉባኤው ተመክሮበታል ።