ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በትናንትናው ዕለት ከኳታሩ አሚር ሼክ ታሚም ቢን ሀመድ አል -አሳኒ ጋር በስልክ ውይይት ማድረጋቸው ተገለጸ ።
ሁለቱ መሪዎች በውይይታቸውም በኢትዮጵያ እና ኳታር ትብብርና ግንኙነትን ይበልጥ ለማሳደግ በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ መምከራቸው ነው የተገለጸው።
በተጨማሪም መሪዎቹ የጋራ በሆኑ የተለያዩ ጉዳዮች ላይም ውይይት ማድረጋቸውም ተገልጿል ።
የኳታሩ አሚር ሼክ ታሚም ቢን ሀመድ አልሳኒ በ2008 ዓመት ሚያዚያ ወር ላይ በኢትዮጵያ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወሳል ።
አሚሩ በጉብኝታቸው ወቅትም በኢኮኖሚ፣ በቱሪዝም ፣ በኢንቨስትመንትና የመሠረተ ልማት ግንባታን ጨምሮ ኢትዮጵያና ኳታር በ11 ዘርፎች በጋራ ለመሥራት ስምምነት ፈጽመዋል ።( ምንጭ: ገልፍ ታይምስ )