አብዴፓ ሰሞኑን ሲያካሂድ በቆየው 7ኛ መደበኛ ድርጅታዊ ጉባዔ ኢንጂነር አይሻ መሃመድን የአፋር ብሄራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ/አብዴፓ/ ሊቀመንበር በማድረግ መረጠ ።
አብዴፓ የአፋር ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባን ደግሞ የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር አድርጎ መርጧል።
አብዴፓ በተጨማሪም የፓርቲውን 11 የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ምርጫን አካሂዷል ።
ከህዳር 23 ጀምሮ በሰመራ ሲካሄድ የቆየው የአብዴፓ 7ኛ መደበኛ ድርጅታዊ ጉባዔም ባለፉት አመታት በክልሉ በነበረው አፈፃፀም እና በወደፊት የልማት አቅጣጫዎች ላይ ትኩረት በማድረግ ባለ 9 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ጉባኤው ተጠናቋል ።
የአብዴፓ ሥራ አስፈጻሚ አባላት ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል ።
1.ኢ/ር አይሻ መሃመድ
2.አቶ አወል አርባ
3.አቶ ኢብራሂም ዑመድ
4.አቶ አህመድ ሱልጣን
5.ወ/ሮ ዘሃራ ዑመድ
6.አቶ መሃመድ ሃሠን
7.አቶ መሃመድ ጠይብ
8.አቶ ጣሃ አህመድ
9. አቶ ዓሊ ሁሴን ዌኢሳ
10. አቶ ኤላማ አቡበከር
11. አሊ ሁሴን ዑመር የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል በመሆን ተመርጠዋል።