የፌዴሬሽን ምክር ቤት በ’ማንነቴ ይታወቅልኝ’ ጥያቄዎች ምክንያት የሚከሰቱ ግጭቶችን ለመከላከል የሚያስችል ፈጣን ምላሽ እንደሚሰጥ ገለጸ።
ምክር ቤቱ በማንነት ጉዳዮችና የጥያቄዎች አፈታት ላይ የሚያተኩር ስልጠና እየሰጠ ነው።
የምክር ቤቱ አፈ-ጉባዔ ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም የ’ማንነቴ ይታወቅልኝ’ ጥያቄዎች ምላሽ አሰጣጥ ውስንነት እንደነበረ ገልጸዋል።
በመሆኑም በአሁኑ ወቅት በማንነት ጥያቄዎች ላይ የማይመለከታቸው አካላት እጃቸውን በማስገባት ግጭት እንዲፈጠር እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
”ህገ-መንግስታዊ ስርዓት እንዲሰፍንና የህግ የበላይነት እንዲከበር በህገ-መንግስቱ አንቀጽ 62 በተሰጠን ስልጣን መሰረት ለጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ እንሰጣለን” ብለዋል።
የፌዴሬሽን ምክር ቤት እስካሁን 76 ብሔሮች ዕውቅና ያገኙ መሆኑን የገለጹት ወይዘሮ ኬርያ በቀጣይ የ’ማንነቴ ይታወቅልኝ’ ጥያቄዎች ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በጠበቀ መልኩ ምላሽ እንደሚያገኝ አረጋግጠዋል። (ኢዜአ)