ፍርድ ቤቱ አብዲ መሐመድ ኡመርና ሌሎች ተጠርጣሪዎች ላይ ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግ ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀናት ጊዜ ፈቀደ ።
መርማሪ ፖሊስ በዛሬው ዕለት በተካሄደው ችሎት ቀደም ሲል በጅምላ የተቀበሩ ሰዎችን ከቦታው አንስቶ በክብር እንዲያርፍ የማድረግ ሥራዎችን ለማከናወን ተጨማሪ ጊዜ እንደሚያስፈልገው ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል ።
ፖሊስ እያደረገ ባለው ምርመራ በጅምላ ተገድለው ተቀብረዋል የተባሉ 200 ሰዎችን በተመለከተ ተጨማሪ የሰዎች የቃል ምስክርነትን ለመሰብሰብ ተጨማሪ ቀናት አስፈላጊ መሆኑንም ለፍርድ ቤቱ አሳውቋል ።