የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት መከላከያ ጥላ እንዲነሳ ተጠየቀ

የላሊበላ  ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ከዝናብና ፀሃይ ለመከላከል የተሠራው ጥላ እንዲነሳ  ተጠየቀ ።

ለዋልታ አስተያየታቸውን የሠጡት የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ደብር ኃላፊ እንደገለጹት  ከዝናብና ፀሃይ ለመከላከል የተሠራው ጥላ ከጥቅሙ ይልቅ  ጉዳቱ በማመዘኑ  መነሳት  እንዳለበት  ተናግረዋል ።

የላሊበላ ደብር የቅርስ ክፍል አስተዳዳሪ ደጉ ቀኝ ጌታ በላይ እንደገለጹት  ከዛሬ አምስት ዓመት  በፊት  ጀምሮ  ጥላው እንዲነሳ አቤቱታ ብናቀርብም  ምላሽ  ሳይሠጠን  ቆይተናል ብለዋል ።

የላሊበላ መከላከያ ጥላን በተመለከተ  በተለያዩ ጊዚያት  ባለሙያዎች ጥናት  አድርገው  ጥላው እንዲነሳ  ምክር ቢሠጡም  እስካሁን  ተግባራዊ አለመደረጉ የሚያሳዝን መሆኑን አስተዳዳሪው  ተናግረዋል ።

የላሊበላ ቅርስ ላይ  ከፍ ያለ ጉዳት  ከደረሰ በኋላ  ከመቆጨትና የታሪክ  ተጠያቄ ከመሆንም  ከወዲሁ እርምጃ  መወሰድ እንዳለበት አስተዳዳሪው አጽዕኖት ሠጥተው ተናግረዋል ።

የላሊበላ  አብያተ ክርስቲያናትን ለመጎብኘት የሚመጣው ቱሪስት ከጊዜ  ወደ ጊዜ  እየጨመረ  መምጣቱም ተጠቁሟል  ።