ለዶክተር ነጋሶ የቀብር ሥነ ስርዓት ብሄራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ተቋቋመ

ለቀድሞው የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ የቀብር ሥነ ስርዓት ብሄራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ተቋቁሞ ስራ ጀምሯል።
ብሄራዊ አስተባባሪ ኮሚቴው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት፣ ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ ከመከላከያ ሚኒስቴር፣ ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽንና ከቤተሰቦቻቸው የተውጣጣ ነው ተብሏል።
የገንዘብ ሚኒስትር ዲኤታና የብሄራዊ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዶክተር ኢዮብ ተካልኝ እንዳሉት፤ የዶክተር ነጋሶን የቀብር ስነ ስርአት ለማስፍፀም ኮሚቴው ስራ ጀምሯል።
ኮሚቴው በስሩ ሶስት ንዑሳን ኮሚቴዎች፤ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚመራ የዝግጅት፣ በገንዘብ ሚኒስቴር የሚመራ የሎጂስቲክስ እንዲሁም የደህንነትና ጥበቃ ኮሚቴዎች ስራቸውን ጀምረዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።