ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የአሸንዳ ክብረ በዓል ላይ ለመገኘት በዛሬው ዕለት መቐለ ገብተዋል፡፡
ፕሬዝዳንቷ አሉላ አባነጋ አየር ማረፊያ ሲደርሱ በትግራይ ክልል ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልና በሌሎች የክልሉ አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡
የአሸንዳ በዓል በትግራይ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የሰላም፣ አንድነትና ልማት ተምሳሌት” በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ይገኛል፡፡
በትግራይ ክልል በነሃሴ ወር የሚከበረው የአሸንዳ፣ ማሪያ እና ዓይኒ-ዋሪ በዓላት የክልሉን ባህል፣ ትውፊትና የቱሪዝም መስህቦች በማስተዋወቅ ረገድ የላቀ ሚና እንዳለው ይነገራል፡፡