ኢትዮጵያና ሶማሊያ ከአራት አሥርት ዓመታት በኋላ የንግድ በረራ ጀመሩ

ኢትዮጵያና ሶማሊያ ከ4 አስርት አመታት በኋላ የንግድ በረራ መጀመራቸዉ ተገለጸ።

የኢትዮጵያ አውሮፕላንም ቅዳሜ ዕለት የመጀመሪያውን በረራ ወደ ሶማሊያዋ መዲና ሞቃዲሾ ማድረጉ ተሰምቷል።

የበረራዉ መጀመር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ከቀጠናዉ ሀገራት ጋር የጀመሩትን የሰላም ሂደት ከማጠናከሩም ባለፈ ምስራቅ አፍሪካን በምጣኔ ሃብት ለማዋሃድ የሚደረገውን ጥረትም ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግር ነው ተብሎለታል።