መስፍን ጣሰው አዲሱ የአየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ተሾሙ

መስፍን ጣሰው

መጋቢት 15/2014 (ዋልታ) መስፍን ጣሰው አዲሱ የአየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆነው መሾማቸውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ።

አዲሱ ተሿሚው በኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ38 ዓመታት በላይ ያገለገሉ መሆናቸውም ተጠቁሟል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወልደ ገብረማርያም ባጋጠማቸው የጤና እክል ምክንያት ከኃላፊነታቸው በፈቃዳቸው መልቀቃቸውን በትላንትናው እለት አየር መንገዱ ማስታወቁ ይታወሳል።

በትዕግሥት ዘላለም

ለፈጣን መረጃዎች፦

ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW

ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth

ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

ቲዊተር https://twitter.com/walta_info

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!