በአማራ ክልል በአንድ ጀምበር 249 ሚሊየን ችግኞች መተከላቸውን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ

ሐምሌ 15/2013 (ዋልታ) – በአማራ ክልል በአንድ ጀምበር 249 ሚሊየን ችግኞች መተከላቸውን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡

ይህም ለመትከል ከታሰበው 247 ነጥብ 8 ሚሊየን ችግኝ በላይ መሆኑን ቢሮ አስታውቋል።

የችግኝ ተከላው በ24 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በ157 ወረዳዎች መካሄዱም ተገልጿል።

(በምንይሉ ደስይበለው)