ወታደራዊ ስልጠና የወሰዱ ወጣቶች ምረቃ በደብረ ማርቆስ

ነሐሴ 27/2013 (ዋልታ) የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በሁለተኛ ዙር ወታደራዊ ስልጠና የወሰዱ ተጠባበቂ ወጣቶችን እያስመረቀ ነው።

ከወታደራዊ ሰልጣኝ ወጣቶች መካከል 35ቱ ሴቶች ሲሆኑ፣ ሰልጣኞቹ የሀገር አንድነትን ለማፍረስ የመጣውን አሸባሪውን የህወሃት ቡድን ለመቅበር ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የአባቶቻችን ልጆች ነን፤ የሀገር ህልውና ሊያፈርስ የመጣውን ሃይል በጀግንነት ለማንበርከክ ዝግጁ ነን ሲሉ ያላቸውን ቁርጠኝነት መግለፃቸውን ኢፕድ ዘግቧል።