ሚያዝያ 13/2014 (ዋልታ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከመገናኛ ብዙኃን አመራሮች ጋር በጋራ መስራት የሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ምክክር እያካሄደ ነው።
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ኮሚሽኑ በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋትን ለማምጣት የሃይማኖት መሪዎችና የሀገር ሽማግሌዎች ጸሎት እንዲያደርጉ በማድረግ ሥራ መጀመሩን አንስተው አሁንም ውጤታማ ሀገራዊ ምክክር ማድረግ እንዲቻል ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመወያየት ግብዓት እየሰበሰበ መሆኑን ተናግረዋል።
የመገናኛ ብዙኃንም ሀገራዊ የምክክር መድረኩ ስኬታማ እንዲሆን ቁልፍ ሚና የሚጫወት በመሆኑ ከመገናኛ ብዘኃን ጋር እንዴት በጋራ መስራት ያስችላል የሚለውን መመካከር ያስፈልጋል ብለዋል።
ፕሮፌሰር መስፍን የምክክር ኮሚሽኑ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ እየሄደበት ስላለው ቅድመ ዝግጅትና ትግበራ ገለጻ አድርገዋል።
በመስከረም ቸርነት
ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!