ሰኔ 29/2013(ዋልታ) – የክብርት ዶክተር አበበች ጎበና አስከሬን ከመኖሪያ ቤታቸው ወደ መስቀል አደባባይ ሽኝት እየተደረገለት ይገኛል፡፡
የክብርት ዶክተር አበበች ጎበና የቀብር ስነ-ሥርዓት በዛሬው ዕለት ከቀኑ በ9 ሰዓት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል።
በመርኃግብሩ መሰረት ከረፋድ 3 ሰዓት ጀምሮ እስከ 5 ሰዓት በመኖሪያ ቤታቸው የአስክሬን ሽኝት መርኃግብር እየተከናወነ ይገኛል፡፡
ከቀኑ 6 ሰዓት እስከ 8 ሰዓት በመስቀል አደባባይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ቤተሰቦቻቸው በሚገኙበት አሸኛኘት እንደሚደረግ ከአበበች ጎበና የህጻናት ክብካቤና ልማት ማህበር ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።