ግንቦት 12/2016 (አዲስ ዋልታ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው ዕለት የተለያዩ ሹመቶችን ሰጡ።
1. ኢንጂነር አይሻ መሀመድ የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር፣
2. አብርሃም በላይ (ዶ/ር) የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና
3. መሀመድ እንድሪስ (ዶ/ር) በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ከግንቦት 13 ቀን 2016 ዓ.ም መሾማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል።