ምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤውን የፊታችን ቅዳሜ ያካሂዳል

ሐምሌ 08/2013 (ዋልታ) – የአዲስ አበባ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን የፊታችን ቅዳሜ   እንደሚያካሂድ ገለጸ፡፡

የምክር ቤቱ የፕሬስ እና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አዲስአለም እንቻለው ምክር ቤቱ የፊታችን ቅዳሜ በሚያካሂደው 8ኛ አመት 3ኛ መደበኛ ጉባኤው የተያዙ አጀንዳዎችን አብራርተዋል፡፡

መደበኛ ጉባኤውም የ2013 በጀት አመት እቅድ አፈጻጸም የማጠቃለያ ሪፖርት ላይ እንደሚመክር ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

በተጨማሪም የ2014 በጀትን ተወያይቶ ያፀድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል፡፡

የአስተዳደሩ የኦዲት ግኝት ሪፖርትም ለምክር ቤቱ እንደሚቅርብና ሰፊ ውይይት እንደሚደረግበት መናገራቸውን የከተማዋ ፕሬስ ሴክሬታሪያት መረጃ ያመላክታል፡፡