በሀረሪ ክልል የተማሪዎች ምገባ ተጀመረ

ሚያዝያ 12/2014 (ዋልታ) በሀረሪ ክልል ባሉ የመንግሥት ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ምገባ ተጀመረ፡፡

በመርኃግብሩ በከተማ እና ገጠር የሚገኙ ከቅደመ መደበኛ እስከ 4ኛ ክፍል ተማሪዎች መካተታቸው ተገልጿል፡፡

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙኽታር ሳሊህ የምገባው ፕሮግራም ባስጀመሩበት ወቅት  እንዳሉት የምገባ ፕሮግራም ዋና ዓላማ ተማሪዎች የተመጣጠነ ምግብ አግኝተው ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዲከታተሉ ለማስቻል ነው።

በተለይም በትምህርት ቤቶች የተማሪዎችን መጠነ ማቋረጥ ለመቀነስና ውጤታማ የመማር ማስተማር ተግባራትን ለማከናወን የምግባ ፕሮግራሙ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አመላክተዋል።

የክልሉ መንግሥት ለተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም ከ35 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት መመደቡን አንስተው በዚህም ከቅድመ መደበኛ እስከ አራተኛ ክፍል ላሉ 35 ሺሕ ተማሪዎች ተጠቃሚ እንደሚደረጉ አብራርተዋል።

የተማሪዎች ምገባ

በክልሉ የተጀመረው የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም ዘለቂነት እንዲኖረው ለማስቻል በክልሉ ከሚገኙ ግብረ ሰናይ ድርጅቶችና ባለሀብቶች ጋር እየተሰራ እንደሆነ ከክልሉ መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

 

ለፈጣን መረጃዎች፦

ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW

ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth

ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

ቲዊተር https://twitter.com/walta_info

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!