በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ያለውን ችግር በትብብር መፍታት አለብን – ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

ሰኔ 22/2014 (ዋልታ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ያለውን ችግር በትብብር መፍታት አለብን አሉ፡፡

የኢትዮጵያ እና የሱዳን ሕዝቦች ወንድማማቾች ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ “በአገራቱ መካከል ብዙ ችግር እንዳለ ምንም ጥርጥር የለውም ነገር ግን ይህንን ችግር ለመጋፈጥ መተባበር አለብን” ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት በአገራቱ መካከል ግጭት ለማባባስ የሚሹ ወገኖች ምንም ጥቅም እንደማያገኙም ነው የገለጹት፡፡