በጥቁር ገበያ ሊሸጥ የነበረ ሽጉጥና ልዩ ልዩ ጥይቶች ከእነ ተጠርጣሪዎቹ እጅ ከፍንጅ ተያዙ


ነሃሴ 3/2013 (ዋልታ) –
የአዲስ አበባ ፖሊስ እና የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በመቀናጀት ባደረጉት ብርቱ ክትትል በጥቁር ገበያ ሊሸጥ የነበረ ሽጉጥና ልዩ ልዩ ጥይቶችን ከእነ ተጠርጣሪዎቹ እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ከእህል ጋር ተደባልቆ ወደ ክልል ሊጓጓዝ የነበረ ጥይት በህብረተሰቡ ትብብር መያዙም ነው የተገለጸው፡፡