የኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ 2ሺህ 526 ተማሪዎች እያስመረቀ ነው

የኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 2ሺሕ 526 ተማሪዎች እያስመረቀ ነው።
በኢትዮጵያ ብቸኛ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የሆነው ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ በዲፕሎማ፣ በመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሁም በሁለተኛ ዲግሪ ያስተማራቸውን 1 ሺሕ 285 ወንድ 1 ሺሕ 241 ሴት በድምሩ 2 ሺሕ 526 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት እያስመረቀ ነው።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ብርሀነመስቀል ጠና (ዶ/ር) የዘንድሮ ተመራቂዎች ሀገር በተለያዩ ችግርች ውስጥ ባለችበት ወቅት መመረቃችሁ በርካታ ኃላፊነት እንድትወስዱ ምክንያት ይሆናችኋል ሲሉ ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም በሁለንታዊ ብልፅግና ሀገርን ማገልገል እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
የዩኒቨርሲቲው የቦርድ ሰብሳቢ የክብር ዶ/ር አባዱላ ገመዳ የምረቃ በዓሉ ለሌላ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግርና ሀገርን ለማገልገል ቁርጠኛ ለመሆን የሚያግዝ ነው ብለዋል።
በዙፋን አምባቸው