ጽሕፈት ቤቱ በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ የማኅበረሰብ አባላት ማዕድ አጋራ

የማዕድ ማጋራት መርኃ ግብር

ሚያዝያ 25/2014 (ዋልታ) ዛሬ ማለዳውን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አጎራባች አካባቢዎች ከተውጣጡ በዝቅተኛ ገቢ ከሚተዳደሩ የማኅበረሰብ አባላት ጋር የማዕድ ማጋራት መርኃ ግብር ተካሄደ።

በማዕድ ማጋራቱ ወቅት በጽሕፈት ቤቱ ቅጥር ግቢ በጓሮ ግብርና አማካኝነት የበቀሉ አትክልቶች እንዲሁም ሰፊ ስፍራ በሌለበት የጓሮ ግብርና ለማካሄድ የሚያስችል መገልገያ መሰጠቱም ተጠቁሟል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሚኒስትር ዴኤታ አለምጸሐይ ጳውሎስ ተሳታፊዎቹን በጽሕፈት ቤቱ ቅጥር ግቢ የሚካሄዱትን የጓሮ ግብርና ሥራዎች በመመልከት ግንዛቤ ወስደው ‘ምግባችን በጓሯችን’ በተሰኘው የጓሮ ግብርና እንቅስቃሴ እንዲሳተፉ ማበረታታቸውንም ከጽሕፈት ቤቱ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።

ለፈጣን መረጃዎች፦

ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW

ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth

ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

ቲዊተር https://twitter.com/walta_info

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!