ግንቦት 15/2014 (ዋልታ) በዛሬው ዕለት 1 ሺሕ 68 ኢትዮጵያዊያን ከሳዑዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ፡፡
በሦስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳዑዲ አረቢያ የመመለስ ሥራ አንድ ሕጻንና 1 ሺሕ 67 ወንዶች መመለሳቸው ታውቋል፡፡
ለተመላሽ ዜጎችም ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ወደ ተዘጋጀላቸው የማቆያ ማዕከላት እንዲሄዱ መደረጉን የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡
እስካሁን በተከናወነው ዜጎችን የመመለስ ሥራ ከ 26 ሺሕ 868 በላይ ኢትዮጵያዊያንን መመለስ መቻሉ ተመላክቷል፡፡
ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW