200 ሺሕ ዶላር የሚገመት ምርት ለወጪ ገበያ ተላከ

ኅዳር 2/2014 (ዋልታ) ሆፕ ሉን ኢትዮጵያ የተሰኘውና በባሕር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ የልብስ ስፌት ላይ የተሰማራው ኩባንያ 200 ሺሕ ዶላር የሚያወጣ የመጀመሪያ ዙር ምርቱን ለወጪ ገበያ ላከ፡፡

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን መረጃ እንደሚጠቁመው የሴቶች አልባሳትን እያመረተ የሚገኘው ኩባንያው አሁን ላይ ለ1 ሺሕ ሰዎች የሥራ ዕድል ሲፈጥር በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ ሲገባ ለ9 ሺሕ ሰዎች ቀጥተኛ ሥራ መፍጠር እንደሚችል ታምኖበታል፡፡

በሌላ ዜና የንግድ ማበረታቻውን አግዋ ለፖለቲካ ፍጆታአውሎ ኢትዮጵያን ከተጠቃሚነት የሰረዘውን የፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር እርምጃ ተፅዕኖ ለመቋቋም አማራጭ ገበያና ምርቶች ላይ ትኩረት እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሳንዶካን ደበበ ተናግረዋል፡፡

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት፦

የአማርኛ ፌስቡክ ገፃችንን ይወዳጁ ይከተሉ

https://www.facebook.com/waltainfo

ከአረብኛ ፌስቡክ ገፃችን ጋርም ይጓዙ

https://bit.ly/3vmjIZR

የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/WALTATVEth

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ

https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

የትዊተር ገፃችንን ይከተሉ

https://twitter.com/walta_info