ችግኝ መትከልና መንከባከብ የካርበን ልቀትን ለመቆጣጠር እንደሚያስችል ተገለፀ

በኢትዮጵያ እየተመናመነ ያለውን የደን ሽፋን ወደ ነበረበት ለመመለስ እና ረባዳ ቦታዎችን በደን ለመሸፍን የሚደረገው የክረምቱ መርሃ ግብር በርካታ መመስሪ ቤቶች ሰራተኞቻቸውን በማስተባበር ችግን እየተከሉ ይገኛሉ፡፡ የሰላም ሚኒስቴር ሰራተኞችም ሁለት ሺ ችግኞችን ተክለዋል፡፡  

የሰላም ሚኒስትሯ ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል በዕለቱ እንደተናገሩት ለኢትዮጵያ ብሎም ለዓለም አሳሳቢ እየሆነ የመጣውን ከፍተኛ የካርበን ልቀት ለመቆጣጠር ችግኝ መትከል እና የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ሥራ መሰራት እንዳለበት ገልጸዋል፡፡

ወ/ሮ ሙፈሪያት እስከ ነሐሴ ድረስ የተለያዩ የሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ ተቋማትን ጨምሮ 5 ሺ ችግኞችን ለመትከል ታስቦ እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

የሰላም ሚኒስቴር ሰራተኞች በበኩላቸው ችግኞችን በመትከል አየተስተዋለ ያለውን የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል እንደሚያስፈልግ በመግለጽ በየጊዜው እየመጡም የተከሉትን ችግኞችን እንደሚንከባኩም ገልፀዋል፡፡