የሚኒስትሮች ም/ቤት በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ተዘጋጅተው በቀረቡ ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳለፈ

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 16ኛ አስቸኳይ ስብሰባ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ተዘጋጅተው በቀረቡ ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡

በዚህም መሠረት የመንግስት ሠራተኞች የሥራ መደቦች ምዘና፣ ደረጃዎች ምደባና የደመወዝ ስኬል ረቂቅ ደንብ፣ ወደ ነጥብ የሥራ ምዘና ሥርዓት ለማሸጋገር በቀረበ ውሳኔ የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ስኬል ጥናትና የውሳኔ ሃሳብ እና የጡረታ አበል ተመን በተመለከተ ለሚኒስትሮቸ ምክር ቤት በቀረቡ ጉዳዮች ላይ በዝርዝር ከተወያየ በኋላ አንዳንድ ማሻሻዎችን በማከል ከሀምሌ 1 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ እንዲውሉ ወስኗል፡፡

(ምንጭ፡-ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት)