የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ 5ኛው ብሔራዊ የገለልተኛ የሳይንሳዊ ጥናት ቡድን ስብሰባ ተጀመረ

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ 5ኛው ብሔራዊ የገለልተኛ የሳይንሳዊ ጥናት ቡድን ስብሰባ በካርቱም ሱዳን መካሄድ ተጀመረ።

የጥናት ቡድኑ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽን ያሳተፈ ሲሆን በግድቡ የውሃ ሙሌትና አለቃቀቅ ዙሪያ የሚመክር ገለልተኛ አካል ነው ተብሏል፡፡

የጥናት ቡድኑ እ.አ.አ ከመስከረም 15 እስከ16/2019 በካይሮ በተደረገው ስብሰባ ወቅት በሦስቱ አገራት የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች በተለዩ አጀንዳዎች ላይ በመወያየት እ.አ.አ ከጥቅምት 4 እስከ 5 2019 በካርቱም በሚካሄደው የሦስቱ አገራት ውሃ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ሪፖርት እንደሚያቀርብ ይጠበቃል።

(ምንጭ፦የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር)