300 ዜጎች ከሳዑዲ አረብያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

ኢትዮጵያዊያን ከሳዑዲ አረብያ ሲመለሱ በኤርፖርት

የካቲት 10/2013 (ዋልታ) – 300 ኢትዮጵያዊያን ከሳዑዲ አረብያ ጂዳ ከተማ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቆንስላ ጉዳዮች ዳይረክቶሬት ጄኔራል ተወካይ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ተገኝተው ለተመላሾቹ አቀባበል እንዳደረጉላቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ አመላክቷል፡፡