የይቅርታና ምህረት አዋጁ ለስድስት ወራት ያህል ሥራ ላይ ይውላል – የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ

የይቅርታና ምህረት አዋጁ  ለስድስት ወራት  ያህል  ሥራ ላይ እንደሚውል  የጠቅላይ  አቃቢ ህግ ዋና አቃቢ ህግ  አቶ ብርሃኑ  ፀጋዬ  ገለጹ ።

ጠቅላይ አቃቢ ህጉ በዛሬው ዕለት በሠጡት መግለጫ እንደተናገሩት ሐምሌ 13 ፤ 2010 ዓም  በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፀደቀው የይቅርታና ምህረት አዋጅ እስከ ግንቦት 30፤2010 ድረስ  የተፈጸሙ ወንጀሎችን  የሚመለከት  መሆኑ ተገልጿል  ።

የይቅርታ የምህረት አዋጁ  በመላ አገሪቱ ተግባራዊ  ሲሆን አዋጁ  ምን አይነት ወንደሎችን እንደሚመለከት  አቶ ብርሃኑ  ፀጋዬ ይፋ አድርገዋል ።

እንደ  አቶ ብርሃኑ ገለጻ  ህገመንግሥታዊ ሥርዓቱን በማፍረስ  የተሳተፉ  ፤ በኃይልና በዛቻ  የመንግሥት ባለሥልጣናትን   በማስፈራራት  ህገወጥ ሥራ የሠሩና ያሠሩ፣ በኢትዮጵያውያን ዜጎችና ተቋማት ላይ ጥቃት የፈጸሙ ፣  የአገሪቱን ሉዓላዊነት በመድፈር  የተሳረፉና የመከላከያ  ሠራዊት  አባላት  እንዲኮበልሉ በማድረግ  ወንጀል በምህረት  አዋጁ  ተጠቃሚ  ይሆናሉ  ብለዋል ።

የወንጀል ድርጊት ፈጽመው የሰው ህይወት ያጠፉና በሙስና ወንጀል ጉዳያቸው እየታየ ያለና  የተፈረደባቸው ወንጀለኞች  ግን  በምህረት አዋጁ እንደማያካትታቸው ዋና አቃቢ ህጉ  በመግለጫቸው አመልክተዋል ።

የምህረት አዋጁ ዋና ዓላማ በአገራዊ ለውጡን  ለማፋጠን ፣ የዴሞክራሲውን ለማሳደግና የፖለቲካዊ  ምህዳሩን ለማስፋት እንዲሁም  የቀጣይ የአገሪቱን  ሰላምና መረጋጋት ለማጠናከር ተግባራዊ  እየተደረገ መሆኑን ዋና አቃቢህጉ  ገልጸዋል ።

መንግሥትያወጀውየይቅርታና ምህረት አዋጅበወንጀል የተከሰሱ ፣ ምርመራ  እየተደረገባቸው ያሉትና የተፈረደባቸውን  ወንጀለኞች  የሚያካትት  መሆኑ ተገልጿል ።