Skip to content
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ሰባተኛ መደበኛ ጉባኤ ከሐምሌ 25/2010ዓ.ም. ጀምሮ እንደሚያካሂድ አስታወቀ፡፡
ለሶስት ቀናት በሚካሄደው ጉባኤ ያለፈው በጀት ዓመት የአስፈፃሚ አካላት፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤትና የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርቶች ላይ በመወያየት እንደሚፀድቅ የክልሉ ምክር ቤት ለኢዜአ በላከው መግለጫ አመልክቷል፡፡
የክልሉን የ2011 በጀት እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል፡፡