መርማሪ ፖሊስ አብዲ ኤሌና ሌሎች አመራሮች 200 ሰዎች እንዲገደሉ ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውን ገለጸ

የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ ሙሓመድናሌሎች የክልሉ ባለሥልጣናት ከ2004 እስከ 2010 ድረስ በሶማሌ ክልል አስተዳደር ላይ ተቃውሞ ያሰሙ 200 የክልሉ ተወላጆች  እንዲገደሉ ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውን ፖሊስ  በምርመራ ሥራው  ማወቁን ገልጿል ።

አቶ አብዲና ሌሎች የሶማሌ ክልል አመራሮች በሥልጣን በነበሩበት ወቅት በተፈጸመው  ኢ -ሰብዓዊ ድርጊት  200  ያህል  ሰዎች  ለስድስት ዓመታት ውስጥ መገደላቸውን  መርማሪ ፖሊስ  ዛሬ  ጠዋት  በተካሄደው  ችሎት ላይ አስረድቷል ።

ፖሊስ  ጉዳዩን  ይበልጥ ለማጣራትና  የሟቾችን ማንነት ለመለየት የተቀበሩባቸውን ሥፍራዎች በውል  ለማየትም  ፍርድቤቱን የ14  ቀን  ተጨማሪ የጊዜ  ገደብ  እንዲሠጠው ጠይቋል ።

የእነ አብዲ ኤሌ ጠበቆች በበኩላቸው ከ2004 ዓም ጀምሮ የተፈጸሙ ወንጀሎች በዚህ ክስ ላይ  መካተት እንደሌለበትና  ለመርማሪ ፖሊስ የ14  ቀን  የጊዜ  ቀጠሮ መፈቀድ እንደሌለበት ተከራክረዋል ።

ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ፖሊስ የክስ መዝገብን በመመልከት መርማሪ ፖሊስ  ሥራውን በተገቢ መልኩ እያከናወነ  እንደሚገኝ  ገልጸዋል ።

በተጨማሪም  በመርማሪ ፖሊስ  የቀረበውና  የሴማሌ  ክልል አመራሮች ፈጽመውታል የተባለውን  የኢ-ሰብዓዊ ድርጊት  በዚህ  መዝገብ  መካተት  የለበትም  የሚለውን  ችሎቱ ውድቅ  አድርጓል ።

በእነ  አብዲ ኤሌና ሌሎች  የሶማሌ ክልል አመራሮች  የተከፈተው ክስን  የፌደራል ፖሊስ  መርማሪ  እንዲያጣ  የተጠቀውን የ14  ቀን የጊዜ  ቀጠሮን ፍርድ ቤቱ በመፍቀድ   ቀጣይ  ችሎቱ  ህዳር  27 እንዲካሄድ  ወስኗል ።