የመጀመሪያው ኢሬቻ የሰላም ሽልማት ስነ ስርዓት በትናንትናው እለት ተካሂዷል።
የኢሬቻ የሰላም ሽልማት በብሄራዊ የባህል የተካሄደ ሲሆን፥ ሀገሪቱ ሰላም እንድትሆን የተጉ ኢትዮጵያውያን ባለውለታዎች የመጀመሪያው የኢሬቻ የሰላም ሸልማት ተበርክቶላቸዋል።
በዚህም መሰረት፦
• የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያሪኮች ብጹዕ ወቅዱስ ማቲያስ
እና ብጹዕ ወቅዱስ መርቆሪዮስ
• አባ ገዳ በየነ ሰንበቶ
• ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሐጂ ኡመር እድሪስ
• የጋሞ የሀገር ሽማግሌዎች የመጀመሪያው የኢሬቻ የሰላም ሽልማት ተሸላሚ ሆነዋል።
• የሶማሌ ክልል የሀገር ሽማግሌ ገራድ ኩልሚዮ መሀመድ ገራድ
በኪነ ጥበብ ዘርፍ
• ጽምጻዊ አሊ ቢራ
• ድምጻዊ መሃሙድ አህመድ እና
• አርቲስት ለማ ጉያ የኢሬቻ የሰላም ሽልማት ተሸላሚ መሆን ችለዋል።(ኤፍ.ቢ.ሲ)