የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚዎች በኤሌክትሪክ ኃይል አለመመጣጠን ምክንያት እየደረሰባቸው ላለው ጉዳት ካሳ ለመክፈል ዝግጁ መሆኑን ገልጿል ።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከአገሪቱ የከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚዎች ጋር በዛሬው ዕለት በካፒታል ሆቴል ውይይት አድርጓል ።
በተካሄደው ውይይትም የከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚዎች በኃይል አለመመጣጠንና መቆራረጥ ምክንያት የተለያዩ የማምረቻ ማሽኖቻቸው እየተበላሹባቸው መሆኑን በወይይቱ ገልጸዋል ።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አብርሃም በላይ በቅርቡ በመብራት መቆራረጥ ምክንያት የሚደርሰውን ችግር ለመቋቋም ከከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ጋር የዋስትና ውል እንደሚገባም ገልጸዋል ።
ኮርፖሬሽኑም የኃይል ተጠቃሚዎች በኃይል አለመመጣጠን ምክንያት የሚደርሱ ጉዳቶችን በጥናት ላይ በተመሠረተ ሁኔታ የካሳ ክፍያን ለመፈጸም ዝግጁ ስለመሆኑ ኃላፊው አመልክተዋል ።
በተለይ የኢንዱስትሪ ፓርኮች እያጋጠማቸው ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥና አለመመጣጠን ችግር የተከሰተው የመብራት መሠረተ ልማትን ከግምት ውስጥ ባላስገባ ሁኔታ የኤሌክትሪክ መሠረት ልማት ዝርጋታ በመካሄዱ መሆኑንም በወይይቱ ተመልክቷል ።