የዘንድሮው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ነጥብ ይፋ ተደረገ

የዘንድሮው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ነጥብ በተፈጥሮ ሳይንስ ለወንዶች 176፣ ለሴቶች 166 እንዲሆን ተወስኗል፡፡ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ ለወንዶች 174፣ ለሴቶች 164 እንዲሆን ተወስኗል፡፡

ለታዳጊ ክልሎች የመግቢያ ነጥቡ በተፈጥሮ ሳይንስ ለወንዶች 166፣ ለሴቶች 156፤ በማህበራዊ ሳይንስ ለወንዶች 164፣ ለሴቶች 154 እንዲሆን ተወስኗል፡፡

ለአካል ጉዳተኞች ደግሞ መስማት ለተሳናቸው በተፈጥሮና በማህበራዊ ሳይንስ ለወንዶች 120፣ ለሴቶች 115፣ ለአይነ ስውራን በማህበራዊ ሳይንስ ለወንዶች 110፣ ለሴቶች 105 እንዲሆን መወሰኑን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡