ጆርጅ ደብሊው ቡሽ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የቀድሞ የአሜሪካ  ፕሬዚዳንት ጆርጅ ደብሊው  ቡሽ (ትልቁ)  ከዚህ  ዓለም  በሞት  መለየታቸው  ተገለጸ  ። 

ትልቁ  ጆርጅ  ቡሽ   በመባል  የሚታወቁት የቀድሞ  የአሜሪካ  ፕሬዚደንት ጆርጅ ደብሊው  ቡሽ በ94  ዓመታቸው  ትናንት  ከዚህ ዓለም  በሞት  መለየታቸውን  ልጃቸው  ገልጸዋል ።   

ጆርጅ ቡሽ 41ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ እኤአ ከ1989 እስከ 1993 በፕሬዚደንትነት ፣ ሁለት ተርም  ደግሞ የፕሬዚደንት  ሬገን  ምክትል በመሆን አገልግለዋል ።       

ትቅሉ ጆርጅ  ቡሽ  ባለፈው  ሚያዚያ  ጀምሮ ሆስፒታል በመግባት የደም ኢንፌክሽን በሽታን ለመከላከል ከፍተኛ  ክትትል እየተደረገላቸው  እንደነበር ተገልጿል ።

ልጃቸው  ጆርጅ ቡሽ  የአባታቸውን  ሞት አስመልክተው በሠጡት መግለጫ አባታችን  በህይወት ከኛ በመለየታቸው  እጅጉን  አንዘናል ብለዋል  ።

ትልቁ ጆርጅ ቡሽ  የትልቅ ስብዕና ትልቅ አባት እንዲሁም ለአገራቸው  ታለቅ ዋጋ የከፈሉ መሆናቸውን  ፕሬዚደንት  ዶናልድ  ትራምፕ  የጆርጅ  ቡሽን  ሞት  አስመልክተው  ለሪፐብሊካን   በትዊተር  ባስተላለፉት  መልዕክት  ገልጸዋል  ።

ጆርጅ ቡሽ  እኤአ  በ1964  ወደ አሜሪካ  ፖለቲካ   የተቀላቀሉ ሲሆን   በ40 ዓመታቸው  የቴክሳስ  የነዳጅ  ንግድ ተቋም  በመመሥረት   ሚሊየነር  መሆን  ችለው ነበር  ።

በሁለተኛ ዓለም ጦርነት ጆርጅ ቡሽ በጦር አውሮፕላን  አብራሪ በመሆን አሜሪካ በጃፓንን  ላይ በከፈተችው   በቦንብ  ድብደባ  ዘመቻ  የተሳተፉና እኤአ በ1944 አውሮፕላናቸው  በጃፓኖች  ተመቶ   በህይወት  መትረፋቸውን   የታሪክ ድርሳናት  ጠቁመዋል ።    

ትልቁ ጆርጅ  ቡሽ  አምስት  ልጆችና  17  የልጅ ልጆችን ፣  ስምንት  የልጅ  ፣ ልጅ ልጅ  ማየት የቻሉና ትልቀ ቤተሰብ  መመሥረት የቻሉ ናቸው  ።