39ኛው የኢጋድ ጉባኤ ተጠናቀቀ

ሰኔ 28/2014 (ዋልታ) በኬንያ ናይሮቢ የተካሄደው 39ኛው የምሥራቅ አፍሪካ በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) አባል ሀገራት ርዕሳነ ብሔራት እና መሪዎች ጉባኤ ተጠናቀቀ፡፡

ጉባኤው ልዩ ልዩ የጋራ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግለጫ በማውጣት መጠናቀቁን ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካን ቡድናቸው ቆይታቸውን አጠናቀው ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል።