39ኛው የኢጋድ ልዩ የመሪዎች ጉባኤ በናይሮቢ እየተካሄደ ነው

39ኛው የኢጋድ ልዩ የመሪዎች ጉባኤ

ሰኔ 28/2014 (ዋልታ) 39ኛው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) ልዩ የመሪዎች ጉባኤ በኬንያ ናይሮቢ እየተካሄደ ነው።

በጉባኤው መሪዎቹ በአካባቢው ሀገራት የሚከሰተውን ድርቅ ማሸነፍ በሚቻልበት ሁኔታ፣ በሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ እንደሚወያዩ ይጠበቃል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የኢጋድ አባል አገራት መሪዎች በጉባኤው ተገኝተዋል።

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW