መጋቢት 7/2014 (ዋልታ) 4 ሚሊዮን 316 ሺሕ ሊትር የምግብ ዘይት በዛሬው ዕለት ወደ ሀገር ውስጥ መግባቱ ተገለጸ፡፡
የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጥላሁን ሳርቃ ለዋልታ እንደገለጹት ባቡር በመጠቀም በአንድ ቀን 4 ሚሊዮን 316 ሺሕ ሊትር ዘይት ወደ ሀገር ውስጥ ገብቷል፡፡
ባቡሩ በአንድ ዙር 2 ሚሊዮን ሊትር እንደሚያጓጉዝ የገለጹት ዋና ሥራ አስፈፃሚው አሁንም ተጨማሪ ዘይት በባቡር በመጓጓዝ ላይ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የገንዘብ ሚኒስቴር 12 ነጥብ 5 ሚሊዮን የምግብ ዘይት በአስቸኳይ ሁኔታ ወደ ሀገር ውስጥ እየገባ እንደሆነ ማሳወቁን መዘገባችን ይታወሳል፡፡
በተስፋዬ አባተ
ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW