በአውስትራሊያ የሚኖሩ የኦሮሚያ ተወላጆች ለሰራዊቱ የሰንጋ ድጋፍ አደረጉ

ጥቅምት 30/2014 (ዋልታ) በአውስትራሊያ የሚኖሩ የኦሮሚያ ክልል ተወላጆች ለአገር መከላከያ ሰራዊት የሰንጋ ድጋፍ አደረጉ።

የመከላከያ ሚኒስትር ዴኤታ ማርታ ሉዊጂ ግምቱ 573 ሺሕ የሚሆን የሰንጋ ድጋፉን ተረክበዋል፡፡

ድጋፉን ያስረከቡት አቶ አብዱልሀኪም ሁሴን ከኢትዮጵያ ውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን አሸባሪውን ቡድን ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለመደምሰስ በጋራ መቆም ይኖርባቸዋል ብለዋል።