ኢትዮጵያ ትናንት አሸነፈች፤ በአሸናፊነትም ትቀጥላለች- ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

ሰኔ 15/2013 (ዋልታ) – ኢትዮጵያ ትናንት አሸነፈች፤ በአሸናፊነትም ትቀጥላለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው እንዳስታወቁት ሰኔ 14 ቀን 2013 ለኢትዮጵያ ታሪካዊ ቀን ነው፡፡

በሀገሪቱ የመጀመሪያ ነፃ እና ፍትሃዊ ምርጫ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ድምፃቸውን ለማሰማት መውጣታቸውንም ገልጸዋል፡፡

ምስሎች አንድ ሺህ ቃላት ይናገራሉ እናም እነሱ በህዝባችን ያለውን ቅንነት፣ ለሰላም እና ለዴሞክራሲያዊ ሂደት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያሉ ሲሉም አመልክተዋል፡፡