የሰላም ጥሪን ለተቀበሉ የቀድሞ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አመራሮች ሹመት ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኦሮሚያ ክልል የመንግስትን የሰላም ጥሪ ለተቀበሉ የቀድሞ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አመራሮች ሹመት ሰጥቷል፡፡

በዚህ መሰረትም፡-

  1. አቶ ያደሳ ነጋሳ————-በቢሮ ሃላፊ ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች አማካሪ
  2. አቶ ኦሮሚያ ረቡማ ———– የኦሮሚያ ክልል ዓቃቤ ሕግ ምክትል ሃላፊ
  3. አቶ ቶሌራ ረጋሳ ————— የኦሮሚያ ክልል ጸጥታና አስተዳደር ቢሮ ምክትል ሃላፊ ሆነው መሾማቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡