ነሀሴ 21/ 2013 (ዋልታ) – የኢትዮ ቴሌኮም የሰሜን ሰሜን ምዕራብ ሪጂን ስራተኞች በማይጸብሪ ግንባር ለሚገኘው ሠራዊት ግምቱ ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ የአይነት ድጋፍ አደረጉ ።
ከተደረገው ድጋፉ ውስጥ ምግብ እና አልባሳት ይገኙበታል ።
የሪጅኑ ሰራተኞች የህልውና ትግሉ በድል እስኪጠናቀቅ ድረስ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ድጋፉን ለሰሜን ጎንደር ሎጅስቲክ ቢሮ ያስረከቡት የኢትዮ ቴሌኮም ሰራተኛ አቶ ሃይለሚካኤል አለሙ ገልጸዋል ።
(በታሪኳ መንግስተአብ)