ጠ/ሚ ዐቢይ የአረንጓዴ ዐሻራ ጥረታችን በርካታ እና ውስብስብ ችግሮችን ለመፍታት ያለመ ነው አሉ

 

ሚያዝያ 9/2014 (ዋልታ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ የጀመረችው የአረንጓዴ ዐሻራ ጥረት የግብርና ምርታማነትን እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንዲቻል በርካታ እና ውስብስብ ችግሮችን ለመፍታት ያለመ መሆኑን አስታወቁ።

የአፈር እና ውኃ ጥምረት ለግብርና ምርታማነት ወሳኝ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እንደ ሀገር ለውኃ እና ለአፈር አያያዝ አሠራሮችን ትኩረት ሰጥቶ መሥራት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት በዓለም በውኃ አቅርቦት ማነስ እና በአፈር መሸርሸር የተነሣ የመሬት መራቆት እየተባባሰ እንደሆነም ጠቅሰዋል።

ለፈጣን መረጃዎች፦

ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW

ቴሌግራም https://t.me/WALTATVEth

ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

ቲዊተር https://twitter.com/walta_info

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!